አቶ አሻግሬ ጀንበሬ
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ
እንደ ሀገር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰሩ ያሉ እና የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ለማስመዝገብ የብዝኃ ኢኮኖሚ ዘርፎች ናቸው ተብለዉ ከተለዩ ዘርፎች የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ አንዱ ሲሆን፡ ይህንን እውን ለማድረግ እንደ ሀገር የአምራች ኢንዱስትሪ ፓሊስና ልዩ ልዩ ስትራቴጂዎችን በማውጣት ተግባራዊ ማድረግ ተችሎአል ፡፡
ከዚህ በፊት በሚዛኑ ትኩረት ያላገኙ የሀገር ውስጥ እና የውጪ ባለሀብቶች በዘርፉ እንዲሰማሩ ማድረግ እና በተመሳሳይ በሀገር ውስጥ ተመርተዉ ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶች እና በሀገር ውስጥ ተመርተዉ በሀገር ውስጥ የመጠቀም ባህል ማሳደግ ተችሎአል ፡፡